• ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ወቅታዊ ጉዳዮች
  • ቪድዮና ድምጾች
  • መጣጥፎች
  • ማህደር
  • ድጋፍ ለመስጠት
  • LIVE
  • Language
    • ትግርኛ
    • English
አትራኖስ ሚድያ
  • ዋና ገጽ
  • ዜና
  • ወቅታዊ ጉዳዮች
  • ቪድዮና ድምጾች
  • መጣጥፎች
  • ማህደር
  • ድጋፍ ለመስጠት
  • LIVE
  • Language
    • ትግርኛ
    • English
አትራኖስ ሚድያ
Home » በሰሃራ በረሃ የሚንቀሳቀሰው የአይ ኤስ አዛዥ መገደሉን የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ተናገሩ
መጣጥፍ

በሰሃራ በረሃ የሚንቀሳቀሰው የአይ ኤስ አዛዥ መገደሉን የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ተናገሩ

July 6, 2021Updated:September 16, 2021No Comments2 Mins Read

የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን በሰሃራ በረሃ አካባቢ የኢስላሚክ ስቴት አዛዥ የነበረው ግለሰብ በፈረንሳይ ወታደሮች መገደሉን አስታወቁ።

አድናን አቡ ዋሊድ አል-ሳሃራዊ እአአ 2015 ላይ የግሬተር ሳሃራ ኢስላሚክ ስቴት የተባለውን ጽንፈኛ ቡድን አቋቁሞ ነበር።

ይህ ቡድን በሰሜን አፍሪካ ቀጠና ለሚደርሱ የሽብር ጥቃቶች ተጠያቂ ሲደረግ ቆይቷል። እአአ 2020 ላይ የፈረንሳይ ዜጎች የሆኑ የእርዳታ ሠራተኞችን ላይ በፈጸመው ጥቃት ስለመግደሉም ተዘግቦ ነበር።

ማክሮን የቡድኑን መሪ ግድያ “በሳህል ከሽብርተኛ ቡድኖች ጋር የምናደርገው ትግል ጉልህ ስኬት ነው” ብለዋል።

  • የአዲስ አበባ የ60ዎቹ የኪነ ህንፃ መለያዎች ‘እድሳት’ እና ያስነሳው ጥያቄ
  • በትግራይ በሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች ላይ የጦር ወንጀል ተፈፅሟል – የመብት ተሟጋች ቡድን
  • የጋናው የቁንጅና ውድድር እና ኢትዮጵያን የወከለችው ተወዳዳሪ
  • የፀጥታው ምክር ቤት የሕዳሴ ግድብን የተመለከተ መግለጫና የኢትዮጵያ አቋም

ሳህል 1.16 ሚሊዮን ስኩዌር ማይል ስፋት ያለው ከደቡብ ሰሃራ በረሃ እስከ ምዕራብ ሴኔጋ፤ ከምዕራብ ሴኔጋ እስከ ምሥራቅ ሶማሊያ የተዘረጋ ሰፊ አካባቢ ነው።

ፕሬዝደንት ማክሮን የአድናን አቡ ዋሊድ አል-ሳህራዊ ግድያ ኦፕሬሽንን በተመለከተ ማብራሪያ አልሰጡም።

የፈረንሳይ መከላከያ ሚንስትር ፍሎረንስ ፓርለይ በትዊተር ገጻቸው፤ ሳህራዊ የተገደለው ባርካህን ኃይል በተባለ የፈረንሳይ ጦር ኦፕሬሽን ነው ብለዋል።

ይህ የፈረንሳይ ኃይል በሳህል በተለየ ደግሞ በማሊ፣ ኒጀር፣ ቻድ እና ቡርኪና ፋሶ እስላማዊ ጽንፈኞችን ይዋጋል።

መከላከያ ሚንስትሯ በተመሳሳይ የቡድኑ መሪ መገደል፤ “ለሽብርተኛ ቡድኑ ትልቅ ውደቀት ነው” ካሉ በኋላ “ትግሉ ይቀጥላል” ብለዋል።

ሳህራዊ በሞሮኮ የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባት ምዕራብ ሰሃራ ውስጥ እአአ 1973 የተወለደ ሲሆን ከሞሮኮ ነጻነትን ለመቀናጀት የፖሊሳሪዮ ግንባር አባል ሆኖ ሲዋጋ ነበር።

ቆይቶም በማግሬብ አካባቢ የሚንቀሳቀሰውን የአል-ቃኢዳ ቡድንን ተቀላቅሎ ሲመራ ነበር። ይህ የማሊ እስላማዊ ቡድን እአአ 2012 ላይ የስፔን ዜግነት ያላቸውን እርዳታ ሠራተኞች አልጄሪያ ውስጥ አግቶ ነበር። በተመሳሳይ ዓመት ማሊ ውስጥ የአልጄሪያ ዲፕሎማቶችን አፍኖ ወስዶም ነበር።

ባለፈው ነሐሴ ወር የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን ስድስት የፈረንሳይ ዜጎች የሆኑ የእርዳታ ድርጅት ሠራተኞች እና ናይጄሪያውን አሸከርካሪዎቻቸው እንዲገደሉ ሳህራዊ ትዕዛዝ ሰጥቷል ብለው ነበር።

ይህ ቡድን እአአ 2019 ላይም በማሊ እና ኒጀር በወታደር ካምፖች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃቶችን ሲሰነዝር ቆይቷል።

እአአ በ2017 ላይ ደግሞ በማሊ በርካታ የአሜሪካ ወታደሮች የተገደሉበትን ጥቃት ያቀነባበረው ይህ በሳህራዊ የሚመራ ቡድን ነበር ተብሏል።

በሳህል ቀጠና ሕገ-ወጥ የሰዎች እና የዕጽ አዘዋዋሪዎች እና ጽንፈኛ እስላማዊ ታጣቂዎች በስፋት ይንቀሳቀሳሉ።

ጂሃዳዊ ጥቃቶችም ወደ ጎረቤት ናይጄሪያ ተዛምተው በርካቶች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

Previous Articleሱዳን ውስጥ በጎርፍ አደጋ ምክንያት ከ80 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ
Next Article በኢትዮጵያ በሁለት ቀናት ውስጥ ከ70 በላይ ሰዎች በኮቪድ መሞታቸው ተመዘገበ

Related Posts

የኑሮ ውድነት ያላቆመው የቁርጥ ሥጋ ፍቅር

September 16, 2021

በ149 ደቂቃዎች ዓለምን የቀየረው የመስከረም 1ዱ የሽብር ጥቃት ምን ይመስል ነበር?

September 16, 2021

የፀጥታው ምክር ቤት የሕዳሴ ግድብን የተመለከተ መግለጫና የኢትዮጵያ አቋም

September 16, 2021

የአዲስ አበባ የ60ዎቹ የኪነ ህንፃ መለያዎች ‘እድሳት’ እና ያስነሳው ጥያቄ

September 16, 2021
Add A Comment

Leave A Reply Cancel Reply

ኣዳዲስ

የኑሮ ውድነት ያላቆመው የቁርጥ ሥጋ ፍቅር

September 16, 2021

በ149 ደቂቃዎች ዓለምን የቀየረው የመስከረም 1ዱ የሽብር ጥቃት ምን ይመስል ነበር?

September 16, 2021

የፀጥታው ምክር ቤት የሕዳሴ ግድብን የተመለከተ መግለጫና የኢትዮጵያ አቋም

September 16, 2021

የአዲስ አበባ የ60ዎቹ የኪነ ህንፃ መለያዎች ‘እድሳት’ እና ያስነሳው ጥያቄ

September 16, 2021

አትራኖስ ሚድያ በዋናነት ኢንግሊዝ አገር ለንደን ከተማ በሚኖሩ ባለሞያዎችና የኮሚኒቲ አባሎች ተነሳሽነትና ድጋፍ የተመሰረት በመሆኑ ዋና መስሪያ-ቤቱ ለንደን ከተማ ሲሆን በእንግሊዝ አገር ሕግ መሰረት ህጋዊ ሰዉነት ኖሮት በUK መንግስት የሚታወቅና ካምፓኒ ሃዉስ ዉስጥ የተመዘገበ ነዉ።

ተጨማሪ ገጾች
  • ስለ እኛ ለማወቅ
  • እኛን ለማግኘት
  • ድጋፍ ለመስጠት
  • ማህደር
  • LIVE
ይከተሉን

መተግበርያችን ይጠቀሙ
© 2023 አትራኖስ ሚድያ

Type above and press Enter to search. Press Esc to cancel.